Ethio Muslim

Ethio Muslim በሽገር ከተማ ስም የሚፈርሱ መስዶችን እቃወማለዉ መስጂድ ፈርሶየሚገነባ ከተማ የለም🇸🇦🇸🇦🇸🇦🇪🇹🇪🇹🇪🇹

በዘንድሮው የ1447 ዓ.ሒ (2018 ዓ.ም) የሐጅ ሥነ-ሥርዓት ላይ የተሳተፉ የኢትዮጵያ ሁጃጆች የሐጅ ስነ-ሥርዓታቸውን በስኬት አጠናቀቁ።​(ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ጄዳ) የዘንድሮው...
31/05/2026

በዘንድሮው የ1447 ዓ.ሒ (2018 ዓ.ም) የሐጅ ሥነ-ሥርዓት ላይ የተሳተፉ የኢትዮጵያ ሁጃጆች የሐጅ ስነ-ሥርዓታቸውን በስኬት አጠናቀቁ።

​(ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም፤ ጄዳ) የዘንድሮው የሐጅ መርሃ-ግብር በስኬት መጠናቀቁን አስመልክቶ በጄዳ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ቆንስል ጀነራል ክቡር አምባሳደር ጣፋ ቱሉ እና የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ክቡር ሼህ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ በተገኙበት ውይይት የተካሄደ ሲሆን፤ ለዚህ ታላቅ ስኬት የበኩላቸውን ከፍተኛ አስተዋጽዖ ላበረከቱ አካላት በሙሉ በጋራ ምስጋና አቅርበዋል።

​የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሀጅና ዑምራ ዘርፍ ሁጃጆችን በጊዜ በመመዝገብ፣ መረጃዎችን በተደራጀ መልኩ ተደራሽ በማድረግ፣ በጤና አጠባበቅና ቀልጣፋ አገልግሎት በመስጠት ባሳየው የላቀ አፈፃፀም ከሳዑዲ አረቢያ የሀጅ እና ዑምራ ሚኒስቴር ከፍተኛውን የአልማዝ (Diamond) ሽልማት በዘንድሮው የሐጅ ማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር ላይ ማሸነፉ የሚታወስ ነው።

ክቡር ሼህ ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ በሳዑዲ አረቢያ የነበራቸውን ይፋዊ የሥራና የሐጅ መርሃ-ግብር አጠናቀው ወደ ሀገራቸው ኢትዮጵያ ተመልሰዋል።

አልሀምዱሊላህ ለዚህም በቃን   የኢትዮጵያ የሀጅና ዑምራ ዘርፍ ለመጀመሪያ ጊዜ በሳውዲ አረቢያ የዳይመንድ (Diamond) ማዕረግ ተሸላሚ ሆነ    የሳውዲ አረቢያ የሀጅ ሚኒስቴር የ1447 ዓ...
31/05/2026

አልሀምዱሊላህ ለዚህም በቃን

የኢትዮጵያ የሀጅና ዑምራ ዘርፍ ለመጀመሪያ ጊዜ በሳውዲ አረቢያ የዳይመንድ (Diamond) ማዕረግ ተሸላሚ ሆነ

የሳውዲ አረቢያ የሀጅ ሚኒስቴር የ1447 ዓ.ሒ የሀጅ ስነ-ስርዓት ማጠናቀቂያና የ1448 ሀጅ ጅማሮ ይፋ ባደረገበት ታላቅ መርሃ-ግብር ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የሀጅና ዑምራ ዘርፍ ባሳየው ከፍተኛ አፈፃፀም እና የላቀ የአመራርነት ክህሎት ለመጀመሪያ ጊዜ የዳይመንድ (Diamond) ሽልማት አሸናፊ ሆኗል።

የሀጅ ሚኒስትሩ ዶ/ር ተውፊቅ ቢን ፈውዛን በተገኙበት እና “ኺታሙሁ ሚስክ” በሚል መሪ ሀሳብ በትናንትና እለት በመካ በተከናወነው በዚህ የእውቅና መድረክ ላይ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ምክትል ፕሬዝዳንትና የዘርፉ ኃላፊ ዶ/ር ሙሀመድ ሳልህ ጀማል ባስመዘገቡት መልካም የሥራ አፈፃፀምና የአመራር ክህሎት ዓለም አቀፍ ሽልማቱን ተቀብለዋል።

ለሽልማቱ ያበቁ ዋና ዋና ስኬቶች

የአል ራህማን እንግዶች (ሁጃጆች) በሰላም፣ በሥርዓትና በተሳካ ሁኔታ የሐጅ ኢባዳቸውን እንዲፈጽሙ ለማስቻል ዘርፉ ያደረገው ከፍተኛ ጥረት ለዚህ ዕውቅና ያበቃው ሲሆን፣ ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች የሚከተሉት ናቸው፦

1) ሁጃጆችን በጊዜ መመዝገብ እና መረጃዎችን በተደራጀ መልኩ ተደራሽ ማድረግ፣
2) የሀጅ ተጓዦችን ለጉዞው በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ ማገዝ፣

3) በጤና አጠባበቅ ረገድ የተደረገው ጥብቅ ክትትል፣
4) ለሁጃጆች የተቀላጠፈና ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት ማቅረብ መቻሉ ናቸው።

በተጨማሪም የዓመታዊው የሀጅ የክብር እንግዶች አቀባበል ስነ-ስርዓት ከትናንት ወዲያ በሚና በሚገኘው ቤተ መንግስት በክብር ተካሂዷል። በዚህ ዓለም አቀፍ ክብር መድረክ ላይ ኢትዮጵያን ወክለው የተገኙት ክቡር ዶ/ር መሐመድ ሳሊህ ከሳዑዲ ዓረቢያ ልዑል አልጋ ወራሽ መሐመድ ቢን ሰልማን ጋር ተገናኝተዋል።

በአህመዲን ጀበል

አንድአንድ ክርስትያን ቤተሰቦች በሰላም ነው ሙልጭ እያደርጋችው ምትሰድቡኝ በተለይ ስለእስዋ ሰለነ ወሒድ ሑሱ ሌሎችም ወንድም እህቶች አላቹ አላህ የመልካም ስራቹን ምንዳ በጀነት የመንዳቹ
30/05/2026

አንድአንድ ክርስትያን ቤተሰቦች በሰላም ነው ሙልጭ እያደርጋችው ምትሰድቡኝ በተለይ ስለእስዋ ሰለነ ወሒድ ሑሱ ሌሎችም ወንድም እህቶች አላቹ አላህ የመልካም ስራቹን ምንዳ በጀነት የመንዳቹ

ማሻአላህ የዘንድሮ  ኢትዮጵያዊያን  ሁጃጆች  ምንም አይነት ቅሬታ ሲያሰሙ በሚዲያ አላየንም የአስተናጋጆቹ መሻሻል ወይንስ የሚዲያ ሽፋን አለማግኘት እናተ ምን ታዘባችሁ?ዘንድሮ ምንም ቅሬታ አ...
30/05/2026

ማሻአላህ የዘንድሮ ኢትዮጵያዊያን ሁጃጆች ምንም አይነት ቅሬታ ሲያሰሙ በሚዲያ አላየንም የአስተናጋጆቹ መሻሻል ወይንስ የሚዲያ ሽፋን አለማግኘት እናተ ምን ታዘባችሁ?ዘንድሮ ምንም ቅሬታ አልሰማንም።

29/05/2026
የአይቮሪ ኮስት ፕሬዝዳንት አልሃሰን ዋታራ በዘንድሮ 2018 ሀጅ ሙዝደሊፋ ጎዳና ላይ ተኝቶ:: ከሀጅ ስነሥርዓቶች ውስጥ እንደ ጎዳና አዳሪ የሚኮንባቸው ቦታዎች አሉ:: ማንም ሳያባርርህ የምት...
28/05/2026

የአይቮሪ ኮስት ፕሬዝዳንት አልሃሰን ዋታራ በዘንድሮ 2018 ሀጅ ሙዝደሊፋ ጎዳና ላይ ተኝቶ:: ከሀጅ ስነሥርዓቶች ውስጥ እንደ ጎዳና አዳሪ የሚኮንባቸው ቦታዎች አሉ:: ማንም ሳያባርርህ የምትሮጥበት, ማንም ሳይሰነዝር ድንጋ^ይ የምትወረውርበት, ቤት እያለህ ጎዳና የምትተኛበት ቦታዎች አሉ:: በእርግጥ የምንሮጠው እመት ሀጀራ የሮጠችበት, ድንጋይ የምንውረውረው ደግሞ ሸይጧንን የምናመልከው ሳይሆን የምንወግረው ተናቂ መሆኑን የምናስብበት ቦታ ነው:: በድንጋይ የወገርከውን ልትፈራው አትችልም::

ሁሉም ሰው የደሃ ኑሮ የሚኖርባቸው ደሃዎችን የሚያስታውስባቸው, ነገ የምጽኣት ቀን እንዴት እንደ ምንቀሰቀስ የምናስታውስባቸው ቦታዎች አንዱ ሙዝደሊፋ ሜዳ ነው:: ልብሱም ስንሞት የምከፈንበት መርፌ እንኳ ያልነካው ከፈን ነው::

በድጋሚ ዒድ ሙባረክ
ክትፎ ላይ ሆኜ ነው::

27/05/2026

Eid Mubarak
🌙🌟عيد مبارك 🌴🐏🌴🐐🌴تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال 🌴🐂🌴🐪🌴كل عم وأنتم بخير🌙🌟
مهندس رمضان

🌙🌙 ዒድ ሙባረክ 🌙🌙عيد مبارك كل عام وانتم بخير 💫✨💫💫✨💫💫تقبل الله منا ومنكم صالح الاعمال اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، الل...
27/05/2026

🌙🌙 ዒድ ሙባረክ 🌙🌙
عيد مبارك كل عام وانتم بخير
💫✨💫💫✨💫💫
تقبل الله منا ومنكم صالح الاعمال

اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،

لاَ إِلَهَ إِلاَّ اللَّهُ،

اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،
وللَّهِ الحمد
ዒድ ሙባረክ!
ለመላው እስልምና እመነት ተከታዮች እና ለማህበራችን አባላትና ደጋፊዎች እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል-አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!
በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር እና የደስታ ይሁንላችሁ። መልካም በዓል!"
በዓሉን ስናከብር የተለመደውን የመረዳዳትን ፣የመተጋገዝን እሴት የበለጠ በሚያጠናክር መልኩ መሆን አለበት ፤ ኡዱህያችን አላህ ሱብሐነሁወተዓላ ባስቀመጠው ኢስላማዊ አደብን በጠበቀ እና (ነቢዩ ሰለላሁዓለይሂወሰለም) ባዘዙን መሠረት ሀይ ልናደርግ ይገባናል ። 1/3ኛውን ለምስኪኖችና ለየቲሞች በመለገስ ይሁን በድጋሚ መልካም በዓል ።
ስልክ
0941987681
0913501394
ሞባይል ባንኪንግ
አንሷር የየቲሞችና አቅመደካሞች መርጃማህበር .
💰💵የማህበሩ አካውንት 💵💰
💶ንግድ =1000528883595
💴ዘምዘም =0021312320101
💷ሂጅራ =1003087020001
ተሌብር
0941987681 ሪያድ ያሲን

በድሮ ጊዜ ነዉ አሉ አንድ ስጋ ቆራጭ ስጋ እየቆረጠ አይኑ ዉስጥ ከስጋ የተቆረጠ አጥንት ይገባበትና በዛን ዘመን እንደ አንድ ትልቅ ዶክተር ይቆጠር የነበረ ወጌሻ ጋር ይሄዳል አሉ። ወጌሻዉም ...
26/05/2026

በድሮ ጊዜ ነዉ አሉ አንድ ስጋ ቆራጭ ስጋ እየቆረጠ አይኑ ዉስጥ ከስጋ የተቆረጠ አጥንት ይገባበትና በዛን ዘመን እንደ አንድ ትልቅ ዶክተር ይቆጠር የነበረ ወጌሻ ጋር ይሄዳል አሉ። ወጌሻዉም አይኑ ዉስጥ ያለዉን አጥንት አየዉና '' ለክፉ የሚሰጥ አይደለም ግን ሁሌ እኔ ጋር እየመጣት አይንህን መታጠብ አለብህ'' ይለዋል።

በዚህ ይስማሙና በየቀኑ እየመጣ እያጠበዉ መኖር ጀመሩ ይህ ስጋ ቆራጭ ሁሌ እየመጣ በሚሸጠዉ ስጋ ይዞለት ይመጣ ነበር ለወጌሻዉ። እንደዚህ እያሉ ብዙ ጊዜ ከቆዩ በኋላ አንድ ቀን የወጌሻዉ ልጅ ይህንን ስጋ ቆራጭ መንገድ ላይ ያገኘዉና '' ወዴት እየሄድክ ነዉ?'' ብሎ ሲጠይቀዉ፤ አባትህ ጋር አይኔን ላሳጥብ እየሄድኩ ነዉ ይለዋል። ይሄ የወጌሻ ልች እስኪ አይንህ ውስጥ ያለዉን አጥንት እኔ ለማዉጣት ልሞክረዉ ብሎ ስያየዉ አይኑ ዉስጥ ያለዉን አጥንት በቀላሉ አወጣለትና '' በቃ ከዛሬ ጀምሮ አባቴ ጋር መሄድ አይጠበቅብህ በማለት ወደ ቤቱ ይመልሰዋል።

ይል የወጌሻ ልጅ ተጫዉቶ ሲያበቃ ወደ ቤት ይሄድና ምሳ ሲጠይቅ ሽሮ ይቀርብለታል። ሁሌ ስጋ የለመደዉ ልጅ በቁጣ መንፈስ '' ዛሬ ስጋ የለም አንዴ'' ብሎ አባቱን ሲጠይቀዉ '' ባክህ ያ አይኑ ዉስጥ አጥንት ያለበት ስጋ ቆራጭ ዛሬ አልመጣም'' ይለዋል። ያኔ ነበር ልጁ '' እሱማ አይመጣም እኮ ከአይኑ ዉስጥ ያለዉን አጥንት አንተ የከበደህን መንገድ ላይ ወደ አንተ እየመጣ አገኘሁትና አወጣሁለት' በማለት ሲነግረዉ። እኔ መቼ ማዉጣት ከበደኝ ሁሌ ሲመጣ ስጋ ስለሚያመጣልን ነበር የተዉኩት ይለዋል።

አየህ ለራሳቸዉ ምቾት ሲሉ የአንተ ህመም ምንም የማይመስላቸዉ ብዙ ሰዎች አሉ ከእነሱ ራቅ።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በአረፋ የሚገኘውን የሁጃጆች ማረፊያ ድንኳን ተዘዋውረው ጎበኙ።•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••ግንቦት 1...
26/05/2026

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በአረፋ የሚገኘውን የሁጃጆች ማረፊያ ድንኳን ተዘዋውረው ጎበኙ።
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ግንቦት 18/2018 ዓ.ል| ዙል ሂጃ 9/1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አረፋ |

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት የክቡር ዶክተር ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በአረፋ የሚገኘውን የኢትዮጵያዊያን ሁጃጆች የማረፊያ ድንኳኖች ተዘዋውረው ተመለከቱ።

ፕሬዝዳንቱ ከድንኳኖች በተጨማሪ ለአረህማን እንግዶች እየቀረበ ያለቅን የምግብና የህክምና አገልግሎት የተመለከቱ ሲሆን ከተጓዦች የአረህማን እንግዶች ጋር ውይይት በማድረግም አጠቃላይ የሀጅ አገልግሎቱን ገምግመዋል።

ሸይኽ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ በዚህ ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት የሀጅ ተጓዦች ኢባዳቸውን በጽሞና እንዲያከናውኑ ለማስቻል ተገቢ ክትትልና ድጋፍ እየተደረገ መቆየቱን ገልፀው ክፍተቶች ከነበሩ ሁጃጆች አፉ እንዲሉ ጠይቀዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንት ጽህፈት ቤት ዋና ኃላፊ ዑስታዝ አቡበከር አህመድ በበኩላቸው የጠቅላይ ምክር ቤቱ ሀጅና ዑምራ ዘርፍ ያከናወናቸው የለውጥ ስራዎች ውጤት ማስመዝገብ መጀመራቸውን ጠቅሰው በቀጣይ ከዚህ በተሻለ መስራት ይጠበቃል ብለዋል።

በቦታው የሚገኙ የአረህማን እንግዶች የጠቅላይ ምክር ቤቱ ፕሬዝደንትና የልዑካን ቡድናቸው አባላት እያደረጉ ላሉት የቅርብ ክትትል ምስጋናቸውን ገልጸው የሁጃጅ ሽኝት፣ አቀባበል እና መስተንግዶ አስደሳች እንደሆነ ገልጸዋል።

በውይይት መርሃ ግብሩ ላይ በምክትል ፕሬዝደንት ማዕረግ የሐጅና ዑምራ ዘርፍ ኃላፊ ዶክተር ሙሐመድ ሷሊህ፣ የስራ አስፈፃሚ አባላት፣ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እና ዑለማዎች የተገኙ ሲሆን ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ ሁጃጆች ዱዓ እንዲያደርጉም ጥሪ ቀርቧል።
•••••••••••••••••••••••••••••••
የኢት/እ/ጉ/ጠ ምክር ቤት ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council
ቴሌግራም | t.me/eiasc1
ትዊተር | https://x.com/eiasc1

Address

Riyadh

Telephone

+966536725022

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethio Muslim posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category