Halaba Sport

Halaba Sport የተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጭ ወቅታዊ መረጃዎችን ያገኛሉ!

ሀላባ ከነማ ሴኔጋላዊውን የተከላካይ አማካይ በዛሬው ዕለት የግሉ አድርጓል።ለ2019 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በጠንካራው ለመቅረብ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ የሚገኘው ሀላባ ከነማ ሴኒጋላዊውን ሴ...
01/08/2026

ሀላባ ከነማ ሴኔጋላዊውን የተከላካይ አማካይ በዛሬው ዕለት የግሉ አድርጓል።

ለ2019 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ በጠንካራው ለመቅረብ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ የሚገኘው ሀላባ ከነማ ሴኒጋላዊውን ሴክ ሳምባን ለማስፈረም ተስማምቷል

ሴክ በሲኔጋል ሊግ ለUS ouakam ከ2022 ጀምሮ በቋሚነት ቡድኑን ሲያገለግል የነበረና ባሳለፍነው የውድድር አመት በ26 ጨዋታዎች በቋሚነት በመሰለፍ 2,100 ደቂቃዎችን መጫወት የቻለ በcenteral midfielder እንዲሁም defensive midfielder ሆኖ መጫወት የሚችል ተጫዋች መሆኑን የተጫዋቹ ስታትስቲክስ ያሳያል።

የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበትን ቀን ታወቀ!የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መስከረም 30 እንደሚጀምር የሊጉ የበላይ አካል የሆነው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበ...
28/07/2026

የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበትን ቀን ታወቀ!

የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ መስከረም 30 እንደሚጀምር የሊጉ የበላይ አካል የሆነው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ይፋ አድርጓል።

17/07/2026
አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ኮንትራቱን አራዝሟል!በውድድር ዓመቱ ወላይታ ዲቻን በመረከብ ወደ ውጤት ጎዳና መመለስ የቻለው አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ከወላይታ ዲቻ ጋር ለቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ለመቆየት ...
15/07/2026

አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ኮንትራቱን አራዝሟል!

በውድድር ዓመቱ ወላይታ ዲቻን በመረከብ ወደ ውጤት ጎዳና መመለስ የቻለው አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ከወላይታ ዲቻ ጋር ለቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ለመቆየት ከስምምነት ደርሷል።

ፈረሰኞቹ ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርመቅዱስ ጊዮርጊስ የሁለት ተጫዋቾችን ዝውውር አጠናቋል።ለ2019 የውድድር ዓመት ቡድኑን ለማጠናከር እንቅስቃሴእያደረጉ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊሶች የሁለት ተጫዋ...
15/07/2026

ፈረሰኞቹ ሁለት ተጫዋቾችን አስፈርመ

ቅዱስ ጊዮርጊስ የሁለት ተጫዋቾችን ዝውውር አጠናቋል።

ለ2019 የውድድር ዓመት ቡድኑን ለማጠናከር እንቅስቃሴ
እያደረጉ የሚገኙት ቅዱስ ጊዮርጊሶች የሁለት ተጫዋቾችን
ዝውውር ማጠናቀቃቸውን ክለቡ ይፋ አድርጓል።

ክለቡን
የተቀላቀሉትም ብሩክ እንዳለ እና ተመስገን ብርሃኑ ናቸው።
አማካይ ብሩክ እንዳለ ከዚህ ቀደም በገላን ከተማ ሲጫወት
የምናውቀው እና በ2016 ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የሊጉን
ዋንጫ ያነሳ ሲሆን ዘንድሮ ከወልዋሎ ጋር የኢትዮጵያ ዋንጫ
ማንሳቱ ይታወቃል።

ሌላኛው የፈረሰኞቹ ፈራሚ ፈጣኑ አጥቂ ተመስገን ብርሃኑ
ነው የእግርኳስ ሕይወቱን በሀዲያ ሆሳዕና ከታዳጊ እስከ
ዋናው ቡድን ያደረገ ሲሆን አሁን ሁለተኛ ክለቡ ይሆን ዘንድ
ቅዱስ ጊዮርጊስን መርጧል።

ተጫዋቾቹም የሕክምና ምርመራቸውን አጠናቅቀው በይፋ ፊርማቸውን ያኖራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የአሰልጣኞችን ዝቅተኛ የአሰልጣኝነት ፍቃድ በተመለከተ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ውሳኔ አሳልፏል።- በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ የሚሰሩ ዋና ምክ...
14/07/2026

የአሰልጣኞችን ዝቅተኛ የአሰልጣኝነት ፍቃድ በተመለከተ የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ባደረገው ስብሰባ ውሳኔ አሳልፏል።

- በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ላይ የሚሰሩ ዋና ምክትል አሰልጣኞች የካፍ ኤ ላይሰንስ ሊኖራቸው ይገባል። የፕሪምየር ሊግ ቡድኖች ዋና እና ምክትል አሰልጣኝ የመቅጠር ግዴታ የሚኖርባቸው ሲሆን ሁለተኛ (ተጨማሪ) ምክትል አሰልጣኝ መቅጠር ለሚፈልጉ ዝቅተኛ የአሰልጣኝነት ደረጃ የካፍ ቢ ላይሰንስ ይሆናል። ለግብ ጠባቂ አሰልጣኝ ደግሞ ዝቅተኛው ሲ ላይሰንስ በግዴታነት ተቀምጧል።

- የኢትዮጵያ ወንዶች ከፍተኛ ሊግ ለዋና እና ምክትል አሰልጣኝ - ቢ ላይሰንስ ፣ ለግብ ጠባቂ አሰልጣኝ - ሲ ላይሰንስ

- የኢትዮጵያ ሊግ አንድ ለዋና እና ምክትል እንዲሁም ግብ ጠባቂ አሰልጣኝ - ሲ ላይሰንስ

- የኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ ዋና አሰልጣኝ - ቢ ላይሰንስ፣ ምክትል አሰልጣኝ እና የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ - ሲ ላይሰንስ

- የኢትዮጵያ ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ዋና አሰልጣኝ፣ ምክትል አሰልጣኝ እና የግብ ጠባቂ አሰልጣኝ - ሲ ላይሰንስ

- በተጨማሪም በኢትዮጵያ ሴቶች ፕሪምየር ሊግ እና ሴቶች ከፍተኛ ሊግ ላይ የሚወዳደሩ ክለቦች ከዋና እና ምክትል አሰልጣኝ መካከል አንዷ ሴት መሆን ይኖርባታል።

30/06/2026

ትውስታ - የቀይ ዛላ ደጋፊዎችና ተጫዋቾች በክረምት ውድድር-

እናመሰግናለን ዶክተር .!❤🙏
12/06/2026

እናመሰግናለን ዶክተር .!❤🙏

አሁን ላይ ለሀገር ውስጥ እግር ኳስ ፍቅር እንዲኖረን ያደረገው ያኔ እናንተ በጊዜው በውስጣችን የገነባችሁት Mentality ነው ያ ስሜት ነው ዛሬም ድረስ በውስጣችን የቆየው....። ላበረከታ...
11/05/2026

አሁን ላይ ለሀገር ውስጥ እግር ኳስ ፍቅር እንዲኖረን ያደረገው ያኔ እናንተ በጊዜው በውስጣችን የገነባችሁት Mentality ነው

ያ ስሜት ነው ዛሬም ድረስ በውስጣችን የቆየው....። ላበረከታችሁት ሁሉ ትልቅ አክብሮት አለን...

እናመሰግናለን በቀጣይም ከቡድኑ ጎን እንደምትሆኑ ሙሉ ተስፋ አለን።

የሀላባ አምባሰደሮች እየመጡ ነው ........🥇🏆
10/05/2026

የሀላባ አምባሰደሮች እየመጡ ነው ........🥇🏆

Address

Cape Town

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Halaba Sport posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share