ወሎ Times

ወሎ Times **ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር**

ሀናን አብዱከአርከባስ እስከ ሀየበል....አቀለጠችውበወሎየ ቋንቋ በወለዬ ባህል ያጌጠቸው ሀናን አብዱ ሙዚቃን በሚገባው ቋንቋ እያናገረችው ትገኛለች። ሀኒቾ ትችላለች ብቻ አይደለም ያው መቸስ ...
20/02/2026

ሀናን አብዱ
ከአርከባስ እስከ ሀየበል....አቀለጠችው
በወሎየ ቋንቋ በወለዬ ባህል ያጌጠቸው ሀናን አብዱ ሙዚቃን በሚገባው ቋንቋ እያናገረችው ትገኛለች። ሀኒቾ ትችላለች ብቻ አይደለም ያው መቸስ የመነን ዘር አይሸጥ አይመነዘር ነውና ነገሩ ወሎን የጥንት ወዙን ሳይለቅ በገምሻራ ቁመናዋ በብርቱ አንደበቷ ከፍ አድርገዋለች።
በርቺ ለማለት ነው ጥሎብኝ ጅስሜ ከዚህ በላይ ከአወራሁ አይችልም።

ሰባት ወሎ መጀን እጣክፍልሽን 10 ያድርገው

27/01/2026

ፈጥኖ ደራሹ ጤና መድህን !

ህይዎት መልከ ብዙ ናት፡፡ የሰው ልጅ በህይዎት ውጣ ውረድ ውስጥ ብዙ አይነት ፈተናዎች ይገጥሙታል፡፡ ህይዎቱንም ለማስተካከልና የተሻለ ኑሮ ለመኖር መውደቅ ፣መነሳት ማግኘትና ማጣት ይጋረጡበታል፡፡

የሀገሬው ብሂል እንደሚተርተውም ‹‹ ጎኔን ከምድር አይኔን ከማገር አታውለው›› እንዲሉ አበው ለሰው ልጅ የተሟላ ጤና እጅግ መሳኝ ነው፡፡ ነገር ግን ባያጋጣሚ ጤናችን ቢታዎክ ደግሞ በጤና መድህን መታከምና መፈወስ ይቻላል፡፡

ጤና መድህን ትርፍን መሰረት ያላደረገ፣ ለዜጎች የጤና ዋስትና የሚሰጥ ነው፡፡ የጤና መድህን አባል ለመሆን አሰቀድመን በከፈልነው አነሰተኛ የገንዘብ መዋጮ መሰረት የጤና እክል የገጠማቸውን ግለሰብ ወይም ቤተሰብ ለህክምና የሚያወጡትን ወጭ በመቀነስ በተቋቋመው የጤና ፈንድ አማካኝነት ወጭን በመጋራት እንደ አቅም ማውጣት እንደ ህመማችን መታከም የሚያስችል የኑሮ ምርኩዝ ነው፡፡

ጤና መድህን ካሉት ዘርፈ ብዙ ጥቅሞች መካከል በማህበረሰቡ መካከል የጋራ መስተጋብርን መፍጠር መቻሉ ነው፡፡ ህክምና ባስፈለገ ጊዜ ከልመና ወይም ከእርዳታ ነፃ ያወጣናል፣ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ዜጎች ፈጥኖ ደራሽም ነው፡፡

ዜጎች ጤናማ በሆኑበት ወቅት የጤና መድህን ተጠቃሚ ከሆኑ የጤና ችግር ቢገጥማቸው ከስጋት ነፃ በመሆን ቀድመው በከፈሉት ተመጣጣኝ ክፍያ የተሸለ የጤና ህክምናዎችን በማግኘት እራሳቸውንና ቤተሰቦቻቸውን ማሳከም ይችላሉ፡፡

በሀገራችን የጤና መድህን ለመተግበር በ1986 ዓ.ም የወጣ የጤና መረጃ ያመላክታሉ፡፡ አንድ የጤና መድህን አባል ወይም ተጠቃሚ ለመሆን በሚያገኘው ገቢ ልክ ክፍያ ይፈፅማል፡፡ በዚህም መሰረት ሶስት የጤና መድህን አይነቶች አሉ፡፡

የመጀመሪያው ማህበረሰብ አቀፍ ጤና መድህን ሲሆን ይህ መድህን በአነስተኛ ገቢ የሚተዳደሩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነው፡፡ ከፍተኛ ቁጥር ያለውን የገጠሩን የማህበረሰብ ክፍልን የሚሸፍንና ሰፊውን ክፍል ይዞ ተደራሽ የሚያደርግ ነው፡፡

ሁለተኛው የመድህን አይነት ማህበራዊ ጤና መድህን ነው፡፡ ይህ በአብዛኛው ጊዜ በተለይ በመንግስት ሠራተኞችና በጡረተኞች ዘንድ የጤና ወጪ የሚጋራ ሲሆን 25 በመቶ የሆነውን የማህበረሰብ ክፍል ይሸፍናል፡፡ ሶስተኛው ደግሞ የግል የጤና መድህን ነው፡፡ ይህ በግል ደረጃ ግለሰቦች የጤና ኢንሹራንስ ወይም መድህን የሚገቡበት ስርዓት ሲሆን ብዙ ጊዜ ለትርፍ የተቋቋመ የጤና መድህን አይነት ነው።

የጤና መድህን ተጠቃሚዎች የጤና እክል ሲገጥማቸው ውል ከወሰዱ የጤና ተቋማት ላይ ያለ ገደብ የፈለጉትን ህክምና ይታከማል፡፡ ያለ ተጨማሪ ወጭ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ፡፡

የአማራ ክልል ጤና መረጃ እንደሚያመለክተው ባሳለፍነው ዓመት በጤና መድህን ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎችን ተጠቃሚ አደርጓል፡፡ መንግስትም የተጠቃሚውን አገልግሎት የበለጠ ለማሳለጥ በመንግስት ድርጅቶች፣ የእርዳታ ድርጅቶች እንዲሁም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ሀብት ያሰባስባል፡፡

የመድሃኒት አቅርቦት እጥረትን ለመፍታት በሀገር ውስጥ እንዲመረት ለፋብሪካዎች ግንባታ ድጎማ እያደረገ ነው፡፡ ይህም የጤና መድህን ያመጣው ትሩፋት ነው፡፡

በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ያሉ ዜጎችን ታሳቢ ያደረገ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥበት አሰራር በመዘርጋት ጤናማና ደስተኛ ዜጋ ማብዛት የብልፅግና ፓርቲ ትኩረት ነው፡፡
ይህን ለማሳካትና የጤና መድህን ሽፋን በመላ ሀገራችን እንዲዳረስ አሰራርን በማዘመን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ደረጃውን የጠበቀ የጤና መድህን ሽፋን ተጠቃሚ እንዲሆን እየተሰራ ነው፡፡
~•~•
🕊ሰላም ለሁሉም፤ ሁሉም ለሰላም🕊

"የጎርጎራ ቃልኪዳናችን፤ ለዘላቂ ሰላም እና ለሁለንተናዊ ብልጽግናችን"
•~•~•
ለወቅታዊ ፣ ትክክለኛና አዳዲስ መረጃዎች የፓርቲያችንን የማህበራዊ ገፆች ይወዳጁ።
ትዊተር :- twitter.com/AppAmhara?s=09
ዩቲዩብ :- youtube.com/channel/UCxQ5MOnm-YH514Qdta0Kysg
ቴሌግራም:- t.me/amharaapp
ቲክቶክ፡- tiktok.com/

መልካም ተግባር ነው የባለቤትነት ስሜት መኖሩ ይበል የሚያሠኝ ነው
02/01/2026

መልካም ተግባር ነው የባለቤትነት ስሜት መኖሩ ይበል የሚያሠኝ ነው

22/10/2025
14/09/2025
14/09/2025

ከቀረጥና ከታክስ ነፃ እንዲገቡ ተፈቅዷል ‼

📌የተሰጠው ጊዜ 1 ዓመት ብቻ ነው

በሞተር ኃይል የሚንቀሳቀሱ ጀልባዎች ከቀረጥ እና ከታክስ ነጻ ሆነው እንዲገቡ መፈቀዱን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሐይቆች የቱሪዝም መዳረሻ እንዲሆኑ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ሲባል የገንዘብ ሚኒስቴር በጉምሩክ አዋጅ ቁጥር 859/2006 (እንደተሻሻለ) አንቀጽ 129 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት በንግድ ሥራ ላይ የተሠማሩ ሰዎች በሞተር ኃይል የሚሠሩ የተለያዩ ዓይነት ጀልባዎችን ለአንድ ዓመት ያህል ከማናቸውም ቀረጥ እና ታክስ ነፃ ሆነው ወደ ሀገር ውስጥ እንዲያስገቡ የሚያስችል መመሪያ አውጥቷል።

በዚህም መሠረት መመሪያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር የአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ማናቸውም በንግድ ሥራ ላይ የተሠማራ ሰው ወደ ሀገር የሚያስገባቸው የሚከተሉት ጀልባዎች መሆናቸውን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

1. ፈጣን እና ቅይጥ አገልግሎት የሚሰጡ ለዓሣ ማጥመጃ እና ለአጫጭር ርቀት የመንገደኛ ማጓጓዣ ወዘተ. የሚውሉ አነስተኛ እና መካከለኛ የሞተር ጀልባዎች(outboard motor boats)፤

2. በመካከለኛ ሐይቆች ላይ ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ፤ ለቱሪስት እና ለአደጋ ጊዜ የሚያገለግሉ ፈጣን ጀልባዎች(speedboats)

3. ለቱሪስቶች ጉብኝት አገልግሎት የሚውሉ ግልጽ ወይም በከፊል የተሸፈኑ ጀልባዎች(Tourist excursion boats)

4. ለሰዎች ማጓጓዣ የሚውሉ ጀልባዎች (Ferries)

5. ለጥናት እና ምርምር የሚያገለግሎ ጀልባዎች(Research boats)

6. ለግል አገልግሎት የሚውሉ ጀልባዎች (Private motor boats)

7. በጸሐይ ኃይል እና በኤሌክትሪክ የሚሠሩ ጀልባዎች( Eco boats)

8. ጠፍጣፋ እና ባለ ጣሪያ የሞተር ጀልባዎች (pontoon boats)እና የመሳሰሉት ለሀገራችን ሐይቆች ተስማሚ የሆኑ የሞተር ጀልባዎች ቀረጥ እና ታክስ ሳይከፈልባቸው ወደ ሀገር ሊገቡ ይችላሉ ሲል የገንዘብ ሚኒስቴር ማስታወቁን ኢቢሲ ዘግቧል።

ጉቦና የእጅ ጥምዘዛ አያሳስባትምበሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰራች ሚኒስትር የሾመችው ሀገር… አልባንያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰራች ሚኒስትር በመሾም በዓለም የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች፡፡የ...
12/09/2025

ጉቦና የእጅ ጥምዘዛ አያሳስባትም
በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰራች ሚኒስትር የሾመችው ሀገር…
አልባንያ በሰው ሰራሽ አስተውሎት የተሰራች ሚኒስትር በመሾም በዓለም የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች፡፡

የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኤዲ ራማ ሙስናን ለመታገል በሚል በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) የተሰራች ሚኒስትር በካቢኔያቸው ማካተታቸው አነጋጋሪ ሆኗል፡፡

የሰው ሰራሽ አስተውሎት ስሪት የሆነችው ሚኒስትር 'ዲዬላ' የሚል ስያሜ የተሰጣት ሲሆን፥ 'ጸሀይ' የሚል ትርጉም እንዳለው ተነግሯል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሀገሪቱን ባህላዊ ልብስ ለብሳ የምትታየውን ሚኒስትር ባስተዋወቁበት መልዕክታቸው፥ የጉቦና የእጅ ጥምዘዛ ማስፈራሪያዎች ስጋት የለባትም ነው ያሉት፡፡

የመንግስትን ስራዎች የሚያከናውኑ ተቋማትንና ኩባንያዎችን ለመምረጥ የሚከናወኑ ጨረታዎችን ለመቆጣጠር ኃላፊነት የተሰጣት ሲሆን፥ የመንግስትን ስራዎች ቀልጣፋ ለማድረግና ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ እገዛ እንደምታደርግ ታምኖባታል፡፡

የኤ አይ ስሪቷ ሚኒስትር ዘመኑ የደረሰባቸውን የቴክኖሎጂ ውጤቶች በመጠቀም ከማይክሮሶፍት ኩባንያ ጋር በመተባበር የበለጸገች መሆኗን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል፡፡

በአሁኑ ጊዜ የሰው ሰራሽ አስተውሎት ቴክኖሎጂ ማሽኖች የሰውን የማሰብ ችሎታ የሚጠይቁ ተግባራትን እንዲፈጽሙ እያስቻለ በከፍተኛ ፍጥነት በማደግ ላይ እንዳለ ይነገራል፡።

 #የጀማ ወንዝ...
12/09/2025

#የጀማ ወንዝ...

@ #አባይ ከጉባ ተራራ ግርጌ
12/09/2025

@ #አባይ ከጉባ ተራራ ግርጌ

Address

Dubai

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ወሎ Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ወሎ Times:

Share

Category